Saturday, December 5, 2009
Saturday, November 14, 2009
የአይምሮ ህሙማኖቹ
ሁለት የአይምሮ ህሙማን ሆስፒታል ግቢ ውስጥ ከስዊሚንግ ፑል አጠገብ ዎክ እያደረጉ እያለ በድንገት አንደኛው ስዊሚንግ ፑሉ ውስጥ ተንደርድሮ ይገባና ውስጥ ይቀራል :: የጉዋደኛውን ውሀ ውስጥ መቅረት የተመለከተው ሌላው በሽተኛም ተወርውሮ ገብቶ ጉዋደኛውን ጎትቶ ያወጣውና ደጋግፎ ወደ ህንጻው ውስጥ ሲያስገባው ዶክተሩ በመስኮት ሆኖ ሲመለከት ስለነበር "ከዚህ የበለጠ የመዳን ምልክት የለምና ይህ ሰው ከሆስፒታሉ መውጣት አለበት " ብሎ የአዳነውን ሰውዬ የሆስፒታል መልቀቂያ ወረቀት ማዘጋጀት ይጀምራል ::
በነጋታው ዶክተሩ ጉዋደኛውን ያዳነውን በሽተኛ ቢሮው ያስመጣውና የመልቀቂያ ወረቀቱን እየሰጠው "የምነግርህ ሁለት ዜናዎች አሉ :: አንዱ ጥሩ አንዱ ደግሞ መጥፎ ዜና ነው :: ጥሩው ዜና ትናንትና የፈጸምከው ጀግንነት በጅጉ የሚያስመሰግንህ ነው :: ይህን በማድረግህም የአይምሮህን ጤንነት መመለስ በማረጋገጣችን ሆስፒታሉን እንድትለቅ ወስነናል :: መጥፎው ዜና ደግሞ ትናንት ያዳንከው ጉዋደኛህ ከህንጻው ጀርባ ባለው ብረት ላይ ራሱን በገመድ ሰቅሎ ሞቶ መገኘቱን ......" ሲለው በሽተኛው አቁአርጦት
"ራሱን ሰቅሎ አይደለም ! እኔ ነኝ እንዲደርቅ ያሰጣሁት "
በነጋታው ዶክተሩ ጉዋደኛውን ያዳነውን በሽተኛ ቢሮው ያስመጣውና የመልቀቂያ ወረቀቱን እየሰጠው "የምነግርህ ሁለት ዜናዎች አሉ :: አንዱ ጥሩ አንዱ ደግሞ መጥፎ ዜና ነው :: ጥሩው ዜና ትናንትና የፈጸምከው ጀግንነት በጅጉ የሚያስመሰግንህ ነው :: ይህን በማድረግህም የአይምሮህን ጤንነት መመለስ በማረጋገጣችን ሆስፒታሉን እንድትለቅ ወስነናል :: መጥፎው ዜና ደግሞ ትናንት ያዳንከው ጉዋደኛህ ከህንጻው ጀርባ ባለው ብረት ላይ ራሱን በገመድ ሰቅሎ ሞቶ መገኘቱን ......" ሲለው በሽተኛው አቁአርጦት
"ራሱን ሰቅሎ አይደለም ! እኔ ነኝ እንዲደርቅ ያሰጣሁት "
የማይናከሰው ውሻ
አንድ ሰውዬ የተጨናነቀ ካፌ ውስጥ ይገባና ባይኑ መቀመጫ ሲፈልግ ያለው መቀመጫ አንዲት ትልቅ ውሻ ጉልበትዋ ላይ ያስቀመጠች ወጣት ሴት አጠገብ ብቻ መሆኑን ይገነዘብና ወደልጅትዋ ጠጋ ብሎ ውሻውን በአይነቁራኛ እየተመለከተ "ይቅርታ የኔ እህት ውሻሽ ይናከሳል ?" ብሎ ይጠይቃታል ::
"አይ አይናከስም " ስትለው መቀመጫውን ሳብ አርጎ አጠገብዋ ሊቀመጥ ሲል ውሻው ተንደርድሮ እጁን ይነክስና ትልቅ ስጋ ይቦጭቅለታል :: ሰውየውም በድንጋጤ እሪታውን ካቀለጠ ቦሀላ ወደ ልጅትዋ ዞር ብሎ "ምናባሽ ውሻዬ አይናከስም አላልሽም ?" ብሎ ይጮህባታል ::
ልጅትዋም "እኮ ! ውሻዬ አይናከስም ይሄ የጉአደኛዬ ውሻ ነው !"
"አይ አይናከስም " ስትለው መቀመጫውን ሳብ አርጎ አጠገብዋ ሊቀመጥ ሲል ውሻው ተንደርድሮ እጁን ይነክስና ትልቅ ስጋ ይቦጭቅለታል :: ሰውየውም በድንጋጤ እሪታውን ካቀለጠ ቦሀላ ወደ ልጅትዋ ዞር ብሎ "ምናባሽ ውሻዬ አይናከስም አላልሽም ?" ብሎ ይጮህባታል ::
ልጅትዋም "እኮ ! ውሻዬ አይናከስም ይሄ የጉአደኛዬ ውሻ ነው !"
ቴዲ አፍሮ
ልጁ በግዜ እሚባል ነገር እቤቱ ገብቶ አያውቅም :: ሊነጋጋ ሲል ወይም አድሮ ካልሆነ በቀር በቀንና በምሽት ቤት ውስጥ ታይቶ አይታወቅም :: ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን ከምሽቱ አንድ ሰአት ሳይሆን እቤት መግባት ጀመረ :: አንዴ ሁለቴ ሶስቴ 1 ሰአት ሰአት ሳይሞላ በግዜ እቤት ሲገባ የተመለከቱት እናት "ምነው ልጄ በግዜ መግባት ጀመርክሳ ?" ብለው ቢጠይቁት
"እንዴ እማዬ አልሰማሽም እንዴ ቴዲ አፍሮ እኮ ተፈትዋል !"
"እንዴ እማዬ አልሰማሽም እንዴ ቴዲ አፍሮ እኮ ተፈትዋል !"
ተናዛዡና ቄሱ
አንድ ሽማግሌ ቤተክርስቲያን ገብቶ ንስሀ መግቢያው ቦታ ይቀመጥና ቄሱን እንዲህ ይላቸዋል "አባቴ .. እድሜዬ 80 ነው , አግብቻለሁ , አራት ልጆችና አስራ አንድ የልጅልጆች አሉኝ :: ትናትና ለሊት ሁለት ከተለያዩ የ 18 አመት ሴቶች ጋር ወሲብ ፈጽሜያለሁ :: ከያንዳንዳቸው ጋር ሁለት ግዜ ነው ያደረኩት "
ቄሱ :- "እሽ የኔ ልጅ .... ለመጨረሻ ግዜ ለንስሀ የመጣኸው መቼ ነበር ?"
ሽማግሌው :- "በጭራሽ መጥቼ አላውቅም :: አይሁድ ነኝ "
ቄሱ :- "ታድያ ለምንድነው የምትነግረኝ ?"
ሽማግሌው :- "ይቀልዳሉ ...... ለሁሉም ሰው እየተናገርኩ ነው "
ቄሱ :- "እሽ የኔ ልጅ .... ለመጨረሻ ግዜ ለንስሀ የመጣኸው መቼ ነበር ?"
ሽማግሌው :- "በጭራሽ መጥቼ አላውቅም :: አይሁድ ነኝ "
ቄሱ :- "ታድያ ለምንድነው የምትነግረኝ ?"
ሽማግሌው :- "ይቀልዳሉ ...... ለሁሉም ሰው እየተናገርኩ ነው "
የፍራፍሬ ሌቦቹ
ሁለት ጉዋደኛማቾች የሰው ፍራፍሬ እርሻ ውስጥ በአጥር ዘለው ገብተው ፍራፍሬዎቹን መብላት ሲጀምሩ ባለቤቱ እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ መሳርያውን ደቅኖ ይመጣባቸውና "እንዳትነቃነቁ " ብሎ ያስቆማቸዋል ::
ከዛም "ፍራፍሬ ለመብላት አስባቹ እስከገባቹ ድረስ .. ከምትወዱት ፍራፍሬ እያንዳንዳቹ መቶ ሰብስባቹ ኑ " ይላቸዋል ::
አንደኛው መቶ ወይን ይሰበስብና ይመጣል :: የእርሻው ባለቤትም "በል አሁን ያመጣኸውን ወይን ቂጥህ ውስጥ ክተተው !" ይለዋል :: አማራጭ ስላልነበረው የተባለውን አድርጎ ይታመማል :: ወዲያው ግን ከት ብሎ መሳቅ ይጀምራል ::
"ምናባህ ነው የሚያስቅህ !" ብሎ ባለቤቱ ሲጮኽበት
"አይ ..በጉዋደኛዬ ነው የምስቀው .... ዋተር ሜሎን እየሰበሰበ ነው "
ከዛም "ፍራፍሬ ለመብላት አስባቹ እስከገባቹ ድረስ .. ከምትወዱት ፍራፍሬ እያንዳንዳቹ መቶ ሰብስባቹ ኑ " ይላቸዋል ::
አንደኛው መቶ ወይን ይሰበስብና ይመጣል :: የእርሻው ባለቤትም "በል አሁን ያመጣኸውን ወይን ቂጥህ ውስጥ ክተተው !" ይለዋል :: አማራጭ ስላልነበረው የተባለውን አድርጎ ይታመማል :: ወዲያው ግን ከት ብሎ መሳቅ ይጀምራል ::
"ምናባህ ነው የሚያስቅህ !" ብሎ ባለቤቱ ሲጮኽበት
"አይ ..በጉዋደኛዬ ነው የምስቀው .... ዋተር ሜሎን እየሰበሰበ ነው "
Subscribe to:
Posts (Atom)